በክልሉ ለምግብ ስርዓት ሽግግርና ኒውትሪሽን ፍኖተ-ካርታ ትግበራ ባለድርሻ ተቋማት በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጌታሁን አብዲሳ ገለጹ

በክልሉ ለምግብ ስርዓት ሽግግርና ኒውትሪሽን ፍኖተ-ካርታ ትግበራ ባለድርሻ ተቋማት በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጌታሁን አብዲሳ ገለጹ
‎***

‎(አሶሳ፣ ሚያዚያ 15/2018 ዓ.ም) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለምግብ ስርዓት ሽግግርና ኒውትሪሽን ፍኖተ-ካርታ ትግበራ ባለድርሻ ተቋማት በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጌታሁን አብዲሳ ገለጹ።

‎በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ ለአምስት ዓመታት የሚተገበር የምግብ ስርዓት ሽግግርና ኒውትሪሽን ፍኖተ-ካርታ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር ተካሂዷል።

‎እንደሀገር የምግብ ስርዓት ሽግግርና ኒውትሪሽን ፍኖተ-ካርታ ተዘጋጅቶ በትግበራ ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ ክልሎችም የራሳቸውን ፍኖተ-ካርታ አዘጋጅተው ወደተግባር እንዲገቡ እየተደረገ ነው።

‎በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የምግብ ስርዓት ሽግግርና ኒውትሪሽን ፍኖተ-ካርታ ተዘጋጅቶ ባለድርሻ ተቋማት አመራሮች እና ፈጻሚዎች በተገኙበት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

‎የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ በመርሐ-ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ እንደገለጹት፣ የምግብ ስርዓት ሽግግርን ውጤታማ ለማድረግ ከአስተሳሰብ ጀምሮ መሥራት አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።

‎በክልሉ የምግብ ስርዓት ሽግግርና ኒውትሪሽን ፍኖተ-ካርታ ትግበራ መዘጋጀቱ በዘርፉ ተጨባጭ ውጤት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ያሉት አቶ ጌታሁን፣ ባለድርሻ ተቋማት የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

‎የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በግብርናው ዘርፍ ትልቅ አቅም ያለበት በመሆኑ ይህንን ምቹ አቅም በጋራ ማልማትና መጠቀም ይገባል ብለዋል።

‎የምግብ ስርዓት ሁሉንም የሚመለከት ነው ያሉት አቶ ጌታሁን፣ መቀንጨርን በመከላከል ጤነኛ እና አምራች ዜጋ ለማፍራት የባለድርሻ አካላትን ትብብር ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዋል።

‎#የቤኒሻንጉል_ጉሙዝ_ክልል_የመንግሥት_ኮሙኒኬሽን_ጉዳዮች

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *