ዜና

ወቅታዊ ሪፖርት በወቅቱ ባለማቅረባቸው በ88 የግል መካከለኛ ክሊኒኮች ላይ እርምጃ መወሰዱን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ አስታወቀ ።

ጥራት ያለዉን የጤና አገልግሎት ለማህበረሰቡ ተደራሽ ለማደረግ የመንግስትና የግሉ ዘርፍ በአጋርነት የሚሰሩበትን ስርዓትን መዘርጋቱ ይታወቃል ።

ይሁን እንጂ የግል የጤና ተቋማቶች በአዋጅ ቁጥር አንቅጽ 46 በተቀመጠዉ መሠረት የጤና መረጃን በመመዘገብና ለሚመለከተዉ አካል ሪፖርት የማደረግ ኃላፊነታቸዉን በአግባቡ ባለመወጣታቸዉ አስተዳደራዊ እርምጃ እንደተወሰደባቸዉ የቢሮ የምግብ ፣መድሀኒት፣ ጤና ክብካቤ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፍቃዱ ባንዞ ገልፀዋል።

እነዚህ የግል ጤና ተቋማት ከ1ወር እስከ 9 ወር በተከታታይ ለሚመለከታቸው አካል ሪፖርት ያላቀረቡ በመተከል ዞን ፣በአሶሳ ዞን እና በአሶሳ ከተማ አስተዳደር የሚገኙ መካከለኛ ክሊኒኮች ሲሆኑ የተወሰደዉ እርምጃ ከማስጠንቀቂያ እስከ እገዳ ድረስ መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል ።

እነዚህ ተቋማት በተቀመጠው አሰራር መሠረት እስከ ሚያዝያ 20/2018 ዓ.ም ሪፖርት የማያቀርቡ ከሆነ የተቋማቱን ፍቃድ የመሰረዝ እርምጃዎች ሊከተሉ ስለሚችሉ ተቋማቶች ሊያስቡበት እንደሚገባው ዳይሬክተሩ አሳስበዋል ።

 

 

 

በአገር አቀፍ ደረጃ በተመረጡ ሴክተሮች የተጀመረው የሪፎርም ስራዎችን በክልሉ ጤና ቢሮ ተግባራዊ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች አበረታች መሆናቸው ተገለፀ። ከፊደራልና ከክልል ሲቪል ሰርቪስ ቢሮ የተውጣጡ አባላት ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ የሪፎርም ሥራዎች ያለበት ሁኔታ ገምግሟል።

በመጀመሪያው ዙር ወደሪፎርም ስራ እንዲገቡ ከተመረጡ ተቋማት አንዱ የቤኒሻንጉል ጉሚዝ ክልል ጤና ቢሮ ሲሆን በቢሮው በባለፉት ጊዜያት የተሰሩ ሥራዎች ከፊደራልና ከተለያዩ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የተውጣጡ አባላት በፊደራል ደረጃ የተዘጋጀ ቼክሊስት በመያዝ የቢሮው የሪፎርም ስራ ያለበትን ደረጃ የመመልከትና፣የድጋፍና ክትትል አድርገዋል።

የቢሮው አመራሮችና የቴክኒክ ኮሚቴ አባላትም የቢሮዉን የስራ እንቅስቃሴያቸውን ካቀረቡ በኋላ የድጋፍና ክትትል ቡድኑ እንደሀገር የተጀመረውን ሪፎርም ወደ ሥራ ለማስገባት የተጀመሩ ሥራዎች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል ።

ቢሮው የስራ አካባቢን ምቹ የማድረግ ስራ እየተሰራ መሆኑ፣በጤናው ሴክተር በተለያዬ ደረጃ የሚገኙ አመራሮችን ስልጠና እየተሰጠ መሆኑ፣የሚሰጡ አገልግሎቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጅ ለመደገፍ መሰረት ልማት እየተዘረጋ መሆኑ፣ከክልል እስከ ወረዳ ተናናቢ መዋቅር እየተዘጋጀ መሆኑ፥ የጤና አገልግሎት አሰጣጡ ጥራት ያለው ለማድረግ የተለያዩ ስትራቴጅ ዶክመንቶች መዘጋጀታቸው ጠንካራ አሰራር መሆናቸውን የድጋፍና ክትትል አባላት ገልጸዋል ።

የክትትል አባላት አክለዉም እነዚህ የተጀመሩ ጠንካራ ሥራዎች ተጠናክሮ እንዲቀጥሉ እና የሚቀሩ ስራዎች በፍጥነት እንዲጠናቀቁና የተጠናከረ መረጃዎች ተደራጅቶ እንዲቀመጥ ምክረ ሃሳብ ተሰጥቷል ።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ የፕሮግራም ዘርፍ ምክትል የቢሮ ሀላፊ የተደረገው ድጋፍና ክትትል የተሰሩ ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠልና በአሰራር የተስተዋሉ ተግዳሮቶችን ፈጥኖ ለመቅረፍ የጎላ ድርሻ ስለአለው ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።

መጋቢት 30/2018 ዓ.ም

በክልሉ በሁሉም አከባቢዎች ከሚያዝያ 29-ግንቦት 2/2018 ዓ.ም ድረስ ቤት ለቤት የሚሰጠውን የፖሊዮ ክትባት (bOPV) ዘመቻ ስኬት ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ አለም ደበሎ ጥሪ አቀረቡ ።

የክልሉ ጤና ቢሮ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻን ምክንያት በማድረግ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የንቅናቄ መድረክ አካሂደዋል።

በዚህ መድረክ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ አለም ደበሎ እንዳሉት የፖሊዮ በሽታ ህጻናትን ለአካል ጉዳት ብሎም ለሞት የሚዳርግ አደገኛ በሽታ መሆኑን ገልጸዋል።

በሽታውን ለመከላከል ክትባት ማስከተብ አስፈላጊ መሆኑን ያስገነዘቡት ምክትል ቢሮ ሀላፊው በተለይ ዕድሜያቸው ከአምስት ዓመት በታች የሆኑ ህጻናትን በማስከተብ ሀላፊነት መወጣት እንዳለበት ነው ያሳሰቡት።

በዚህ ዘመቻ ከፖሊዮ ክትባት በተጨማሪ መደበኛ ክትባት ያልወሰዱ ህጻናት እንዲከተቡ፣ክትባት ጀምሮ ያቋረጡ ህጻናት በመለየት የአገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እንዲሁም የፊስቱላ ባሽታን ጨምሮ ለሎች የጤና ፕሮግራሞች በቅንጅት እንደሚሰራም ተገልጸዋል።

በዚህ ዘመቻ ዕድሜያቸው ከአምስት አመት በታች የሆኑ ከ220 ሺ በላይ ህጻናት ተጠቃሚ ይሆናሉ ያሉት ደግሞ በክልሉ ጤና ቢሮ የህብረቱሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ዳይሬክተር የሆኑት አቶ መብራቱ በጉኖ ናቸው።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የጤናው ዘርፍ አጋር አካላት፣ከተለያዩ ሴክተር የተወጣጡ የስራ ሀላፊዎች እንዲሁም ለሎች ባለድርሻ አካላይ በበኩላቸው ለዘመቻው ስኬት የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡም በሰጡት አስተያየት ተናግረዋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ!